Thursday, July 12, 2012

መልክዐ ተክለ ሃይማኖት ሰላም ለፅንሰትከ


   ክፍል ሁለት   መልክዐ ተክለ ሃይማኖት  ሰላም ለፅንሰትከ
             "ሰላም ለፅንሰትከ ወለልደትከ እምከርሥ።አመ ዕሥራ ውረቡዑ ለወርኃ ታኅሣሥ።ተክለሃይማኖት በኩሉ ወበውስተ ኰሉውዱስ ።ናሁ ወጠንኩ ወዕቤ ለስብሓቲከ ሐዲስ ።በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ።"ትርጉም ''ተክለ ሃይማኖት ሆይ አስቀድሞ በማህጸንለተጸነስከው ጽንሰትህና በታህሳስ ሃያ ዐራት ቀን ለተወለድከው መወለድህም ሰላም እላለው በሁሉ ዘንድ የተመሰገንክ ተክለሃይማኖት ሆይ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብዬ አዲስ የሚሆን ምስጋናህን እጀምራለሁ''በክፍል አንድ ጽሑፋችን '' ሰላም ለፅንሰትከ ወለልደትከ እምከርሥ። 

Friday, July 6, 2012

መንፈሳዊውን ከመንፈሳዊው ጋር

     ሚልክያስ ማለት መልእክተኛዬ ማለት ነው:: ነቢዩ ሚልክያስ አራት ምዕራፎች ያሉት የትንቢት መጽሐፍ ጽፏል:: የነበረበት ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት በነእዝራና ነህምያ ዘመን 470-440. መካከል ነው::በትንቢት መጽሐፉ ከጻፋቸው ነገሮች መካከል ስለ ቃል ኪዳን መልእክተኛው ስለ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ የተናገረው ይገኝበታል::<<እነሆ፥ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል . . . >> /ሚል.3:1/::