Saturday, August 11, 2012

መልክዐ ተክለሃማኖት

   ክፍል ሶስት  መልክዐ ተክለሃማኖት
    ሰላም ለዝክረ ስምከ በጥንተ ፊደሉ መስቀል  ስም ክቡር ወስም ልዑል። ተክለሃማኖት ማቴዎስ በዓለ ቀዳማይ ወንጌል ከመ እወድሰከ መጠነ አውሥኦተ እክል። ማዕሠረ ልሳንየ ትፍታሕ ማርያም ድንግል። 
ትርጉ  << የስምሀ መነሻ ፊደል የመስቀል ምልክት ለሆነው እና ክቡር ገናና ለሆነው ስም አጠራርህ ሰላም እላለው የወንጌል ተቀዳሚ ስም ማቴዎስ የተባልክ ተክለሃይማኖት ሆይ እንደ ችሎታዬ አመሰግንህ ዘንድ አንደበቴ ትፈታልኝ ዘንድ ድንግል ማርያምን እማልዳለሁ።  >>