Thursday, December 27, 2012

                               ን ኮ 

                       በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
                  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታህሣሥ 19 ከከበሩት መላእክት አንዱ የሆነው የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክበረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት በመዝሙር በጸሎት በምስጋና በቅዳሴ በዝክር ይከበራል ይታሰባል። የሚከበርበት ምክንያት ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠለሥቱ ደቁቅን ከዕቶነ እሳት(ከነደደ እሳት) ያዳነበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
          ቅዱስ ገብርኤል ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው ብሏል ሉቃ 1፥20 

Monday, October 29, 2012


   ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት ይመለከታታልን ?  ክፍል 6
    ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት ይመለከታታልን?
ከዚህ ቀደም ባቀረብናችው ጽሁፎች  እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም  የጥንተ አብሶ ፍዳ እንደ ማይመለከታት ቅዱሳን አባቶቻችን የተናገሩትን መመልከት ጀምረን ነበር በዚህ ጽሁፋችንም ቀጣዩን ክፍል እንመለከታለን  አምላካችን ልዑል እ ግዚአብሔር የእናቱን በረከት ረድኤት ያሳድርብን አሜን
  ቅዱስ  ኤራቅሊስ  በሃይማኖተ  አበው ምዕራፍ  48 ቁጥር 31  ስለ እመቤታችን ንጽህና ሲመሰክር እንዲህ ይላል 
     « ኢያእመረ እስመ ዘተፈጥረት እምነ ጽቡር ጽሩይ ትከውን  መቅደሶ ለእግዚአብሔር »ትርጉም « የእግዚአብሔር መቅደሱ ማደርያው ትሆነው ዘንድ ከንጹህ አፈር (ዘር)የተፈጠረች  መሆኗን አላወቀም  »

Tuesday, September 11, 2012

ዘመኑን ዋጁ

    የተወደዳችሁ ምእመናን እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ አሸጋገራችሁ
            ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን ለሚገኙ ምእመናን መጪው ጊዜ ምን እንደሚመስል ከገለጠላቸው በኋላ አያይዞ እንዴት መኖር እንዳለባቸው መክሮአቸዋል፡፡ ስለመጪው ጊዜ ሲነግራቸው ‹‹ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና›› ብሏቸዋል፡፡

ዘመነ ሰላም  ያድርግልን  2005

እንዴት መኖር እንዳለባቸው ሲመክራቸው ደግሞ ‹‹እንደጥበበኞች›› በጥበብ መመላለስ እንደሚገባቸው፤ ዳግመኛም ‹‹በጥንቃቄ›› እና ‹‹በመጠበቅ›› እየኖሩ ዘመኑን እንዲዋጁ አሳስቧቸዋል፡፡ (ኤፌ5.15-16) እነዚህ ቁም ነገሮች ለጊዜው በኤፌሶን ላሉ ምእመናን ቢጻፉም ለሁላችን ምክር እና እዝናት የሚሆኑ ናቸውና በየተ
እንመለከታቸዋለን

Saturday, August 11, 2012

መልክዐ ተክለሃማኖት

   ክፍል ሶስት  መልክዐ ተክለሃማኖት
    ሰላም ለዝክረ ስምከ በጥንተ ፊደሉ መስቀል  ስም ክቡር ወስም ልዑል። ተክለሃማኖት ማቴዎስ በዓለ ቀዳማይ ወንጌል ከመ እወድሰከ መጠነ አውሥኦተ እክል። ማዕሠረ ልሳንየ ትፍታሕ ማርያም ድንግል። 
ትርጉ  << የስምሀ መነሻ ፊደል የመስቀል ምልክት ለሆነው እና ክቡር ገናና ለሆነው ስም አጠራርህ ሰላም እላለው የወንጌል ተቀዳሚ ስም ማቴዎስ የተባልክ ተክለሃይማኖት ሆይ እንደ ችሎታዬ አመሰግንህ ዘንድ አንደበቴ ትፈታልኝ ዘንድ ድንግል ማርያምን እማልዳለሁ።  >>  

Thursday, July 12, 2012

መልክዐ ተክለ ሃይማኖት ሰላም ለፅንሰትከ


   ክፍል ሁለት   መልክዐ ተክለ ሃይማኖት  ሰላም ለፅንሰትከ
             "ሰላም ለፅንሰትከ ወለልደትከ እምከርሥ።አመ ዕሥራ ውረቡዑ ለወርኃ ታኅሣሥ።ተክለሃይማኖት በኩሉ ወበውስተ ኰሉውዱስ ።ናሁ ወጠንኩ ወዕቤ ለስብሓቲከ ሐዲስ ።በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ።"ትርጉም ''ተክለ ሃይማኖት ሆይ አስቀድሞ በማህጸንለተጸነስከው ጽንሰትህና በታህሳስ ሃያ ዐራት ቀን ለተወለድከው መወለድህም ሰላም እላለው በሁሉ ዘንድ የተመሰገንክ ተክለሃይማኖት ሆይ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብዬ አዲስ የሚሆን ምስጋናህን እጀምራለሁ''በክፍል አንድ ጽሑፋችን '' ሰላም ለፅንሰትከ ወለልደትከ እምከርሥ። 

Friday, July 6, 2012

መንፈሳዊውን ከመንፈሳዊው ጋር

     ሚልክያስ ማለት መልእክተኛዬ ማለት ነው:: ነቢዩ ሚልክያስ አራት ምዕራፎች ያሉት የትንቢት መጽሐፍ ጽፏል:: የነበረበት ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት በነእዝራና ነህምያ ዘመን 470-440. መካከል ነው::በትንቢት መጽሐፉ ከጻፋቸው ነገሮች መካከል ስለ ቃል ኪዳን መልእክተኛው ስለ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ የተናገረው ይገኝበታል::<<እነሆ፥ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል . . . >> /ሚል.3:1/::

Monday, June 25, 2012

ነገረ መላእክት ክፍል አንድ

 የተከበራችሁ አንባብያን ባለፈው ዝግጅችን ቅዱሳን ?ተፈጥሮአቸውን፤አማላጅነታቸውን፤ጸጋቸውን ፤ክብራቸውን ፤በአጠቃላይ በቅዱሳን  መላእከት ዙሪያ  ቅድሰት ቤተክርስቲያን ያላትን አስተምሮ እና

    መናፍቃን ስለቅዱሳን መላእክት የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ለመዳሰስ  እንሞክራለን ብለን በገባነው ቃል መሰረት ከዛሬ ጀምሮ ይዘን እንቀርባለን አምላከ ቅዱሳን ጸጋውን ያድለን  በስነፍጥረት  ትምህርት ከ22 ነገደ ፍጥረታት መካከል  አንዱ ነገድ  የመላእክት ነገድ ነው (1) 

Tuesday, June 19, 2012

ተራዳሂው መልአክ

              ተራዳሂው  መልአክ
       በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት እና ስርዓት መሰረት በየዓመቱ ሰኔ 12 ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ መታሰቢያውን በታላቅ ድምቀት እናከብራለን ይህም ዕለት አስደናቂው የእግዚአብሔር ቸርነት፤ በመልአኩበቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት የተፈጸሙ ተአምራት እያስብን ሁሉን ማድረግ የሚችለውን፤ አምላክ እናመሰግናለን ።
          ቅዱስሚካኤል የሚለው ስም ቅዱስ እና ሚካኤል የሚባሉ የሁለት ቃላት ውህድ ነው፡;

Wednesday, June 13, 2012

ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት ይመለከታታልን?

ክፍል አምስት ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት ይመለከታታልን?
            ከዚህ ቀደም ተከታታይ ባቀረብናቸው ጽሑፎች ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት እንደማይመለከታት ከብዙ በጥቂቱ ለማየት ሞክረናል ቀጣዩን ጽሑፋችንን ይዘንላችሁ ቀርበናል በአሰተውሎት ማንበቡን እግዚአብሔር ያድለንበክፍል አራት  ጽሑፋችን«ወለደት ድንግል ዘፀንሰቶ እንዘ  ኢተአምር ብእሴ በስጋ ዘፈጠሮ   ለርእሱ ወወለደቶ ዘእንበለ ደነስ ወሕማም ወኢረሰስሐት በሐሪስ ሐፀነቶ ዘእንበለ ፃማ ወድካም ወአጥበቶ ዘእንበለ ድካም ወአልሐቀቶ በሕግ ዘሥጋ  ዘእንበለ  ትካዝ ።»

Monday, May 21, 2012

«ያለ መቃብሩ የመዳን ተስፋ የላችሁም» ለምን ተባለ ?


       «ያለመቃብሩየመዳንተስፋየላችሁም»ለምንተባለ?"ክፍ3                                       
               <<ወአልብክሙ ተስፋ ድኂን ዘእንበለ መቃብሪሁ»                            
        በክፍል ሁለት ጽሑፋችን ሊቀ ጳጳሱ <<ወይ ሰው የነፍሱን ድኅነት ሳያውቅ ይጎዳል >>የሚለውን አባባል ምን ማለት እንደሆነ ተመልክተን ነበር ያቆየነው በዚህ ጽሑፋን ደግሞ  ቀጣዩን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ለሁላችንም ማስተዋሉን ያድለን አሜን

Thursday, May 10, 2012

ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት ይመለከታታልን?


        ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት ይመለከታታልን ክፍል አራት  

     ከላይ በተነሳው ጥያቄ ላይ እስከ ክፍልሶስት ድረስ በተከታታይ ምላሽ ስንሰጥ መቆየታችን ይታወሳል በዚህ ጽሑፋችንም ቀጣዩን ክፍልይዘንላችሁ ቀርበናል እግዚአብሔር አምላክበማስተዋል ማንበቡን ያድለን አሜን
  በቀደሙት ጽሁፎቻችን እመቤታችን የውርስ ኃጥአት እንደማይመለከታት  ከብዙ በጥቂቱ ለመመልከት ሞክረናል በዛሬው ጽሑፋችን ድንግልማርያም የውርስኃጢአት ይመለከታታል  ማለት  በመሰረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምሮ ላይ የሚያስነሳቸውን ተቃርኖዎች ለመመልከት እንሞክራለን ።

Saturday, May 5, 2012

«ያለ መቃብሩ የመዳን ተስፋ የላችሁም» ለምን ተባለ ? ክፍል ሁለት

         «ያለ መቃብሩ የመዳን ተስፋ የላችሁም» ለምን ተባለ ?
 "ወአልብክሙ ተስፋ ድኂን ዘእንበለ መቃብሪሁ»
                              «ያለ መቃብሩ የመዳን ተስፋ የላችሁም»        ክፍል ሁለት
          በክፍል አንድ ጽሑፋችን በአባታችን በቅዱስ ተክለሃይማኖት ገድል ላይ ያለመቃብሩ የመዳን ተስፋ የላችሁም ለምን ተባለ በሚለው ጥያቄ መነሻነት የተወሰኑ ነጥቦችን ተመልክተን በይቆየን አስተላልፈን ነበር በዚህ ጽሁፋችን ቀጣዩን ክፍል እንመለከታለን እግዚአብሔር አምላክ ለሁላችንም ማስተዋሉን ያድለን አሜን
ሁለቱ መነኮሳት ወደ ኢየሩሳሌም ሲጓዙ ከሊቀ ጳጳሱ ጋር ተገናኝተው ሊቀ ጳጳሱ በእንግዳ ተቀባይነት እንዲሁም ከመጡበት ቦታ ታላቅነት አንጻር መጽሐፍ ቅዱሳዊየሆነአክብሮት ሰጥቶ እንደተቀበላቸው ተመልክተናል

Thursday, April 19, 2012

ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት ይመለከታታልን?

ክፍል 3ካለፈው  የቀጠለ ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት ይመለከታታልን? 
    ባለፈው የክፍል 1 እና ክፍል 2 ዝግጅታችን ማስነበባችን ይታወሳል በገባነው ቃል መሰረት ቀጣዩን ይዘን  ቀርበናል መልካም ንባብ      
3.እመቤታ ድንግል ማርያም የውርስ   ኃጢአት አለባት ማለት  የጌታችንን ንጹሐ  ባህሪውን መዳፈር ነው   
ጌታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን ሰው ሲሆን ስጋና ነፍስን ከሰማይይዞ አልወረደም ሰው የሆነው የእኛን ባህሪይ ተዋሕዶ ነውይህን በተመለከተ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይላል"እንግዲህ ልጆቹ በስጋና በደም ስለሚካፈሉ እርሱ ደግሞ በሞት ላይስለጣንያለውንእንዲሽር-እንዲሁ ተካፈለ የአብርሃምን ዘር  ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም''ዕብ2፤14-15

Sunday, April 15, 2012

ትንሳኤ ክርስቶስ

በኩረ ትንሳኤ  ክርስቶስ

       ርስቶስ ተንሥአ እሙታን                   በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን                     አሠሮ ለሰይጣን                            አግአዞ ለአዳም                                    ሰላም                                     እምይእዜሰ                                        ኮነ                                   ፍስሐ ወሰላ

                                  የዕለቱ ምስባክ

 ወተንሥአ እግዚአብሔር             እግዚአብሔርም ከእንቅልፍ            ከመዘንቃህ እምንዋም          እንደሚነቃ ተነሣ              ኃያል ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን    የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኀያል            ወቀተለ ፀሮ በድኀሬሁ                 ሰውጠላቶቹንም በኋላቸው መታ፡፡

  ትርጉም፦
እግዚአብሔርም ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ
የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኀያል  
 ሰውጠላቶቹንም በኋላቸው መታ፡፡
          ትንሳኤ  ክርስቶስ